መዝሙር 103
እረኞች—ስጦታ የሆኑ ወንዶች
(ኤፌሶን 4:8)
-
1. አምላካችን በደግነቱ
እረኞች ሰጥቶናል፤
ምሳሌ ሆነው በማገልገል
መንገድ ይመሩናል።
(አዝማች)
አምላክ ሰጥቶናል ታማኝ ወንዶች፣
እውነተኛ እረኞች።
ለመንጋው ’ሚጨነቁ ናቸው፤
ምንጊዜም አድንቋቸው።
-
2. በርኅራኄ ይይዙናል፣
በፍቅር በመምራት።
ስንጎዳ ይጠግኑናል፣
በቃል በማጽናናት።
(አዝማች)
አምላክ ሰጥቶናል ታማኝ ወንዶች፣
እውነተኛ እረኞች።
ለመንጋው ’ሚጨነቁ ናቸው፤
ምንጊዜም አድንቋቸው።
-
3. ከአምላክ መንገድ እንዳንወጣ፣
ምክር ይሰጡናል።
ሁሌ እንድናገለግለው፣
ያበረታቱናል።
(አዝማች)
አምላክ ሰጥቶናል ታማኝ ወንዶች፣
እውነተኛ እረኞች።
ለመንጋው ’ሚጨነቁ ናቸው፤
ምንጊዜም አድንቋቸው።
(በተጨማሪም ኢሳ. 32:1, 2ን፣ ኤር. 3:15ን፣ ዮሐ. 21:15-17ን እና ሥራ 20:28ን ተመልከት።)