መዝሙር 62
አዲሱ መዝሙር
(መዝሙር 98)
-
1. ዘምሩ ላምላክ፤ አዲስ የውዳሴ መዝሙር።
አውሩ፣ ተናገሩ የሱን ታላቅ ተግባር።
ድል አድራጊ ነው፤ ኃያል ክንዱን አሳይቷል።
ፍትሕን ይወዳል፤
በጽድቅም ይፈርዳል።
(አዝማች)
ዘምሩ!
አዲሱን ዝማሬ!
ዘምሩ!
ያህ ንጉሥ ነው ሁሌ!
-
2. ለንጉሣችን እንዘምርለት በደስታ!
ስሙን አወድሱ፤ ከፍ አ’ርጉት በ’ልልታ።
ሕዝቦቹ ሁሉ ላምላክ በኅብረት ዘምሩ።
መለከት፣ በገናም
ያህን ያመስግኑ።
(አዝማች)
ዘምሩ!
አዲሱን ዝማሬ!
ዘምሩ!
ያህ ንጉሥ ነው ሁሌ!
-
3. ባሕሮችና በውስጣቸው ያለው ሕይወት፣
የምድርም ፍጥረታት እሱን ያወድሱት።
ምድርም ሐሴት ታ’ርግ፤ ወንዞች ሁሉ ያጨብጭቡ።
ተራሮች፣ ኮረብቶች
ክብሩን ያስተጋቡ።
(አዝማች)
ዘምሩ!
አዲሱን ዝማሬ!
ዘምሩ!
ያህ ንጉሥ ነው ሁሌ!
(በተጨማሪም መዝ. 96:1፤ 149:1ን እና ኢሳ. 42:10ን ተመልከት።)