መዝሙር 51
ራሳችንን ለአምላክ ወስነናል!
-
1. የሰማዩ አባት ወደ ልጁ ሳበን፤
የ’የሱስ ተከታዮች ሆንን።
ከአምላክ ታላቅ ዙፋን፣
ፈንጥቋል የ’ውነት ብርሃን።
እምነታችን ጠንክሯል፤
ራሳችንን ክደናል።
(አዝማች)
ወደን ላምላክ ራሳችንን ወስነናል፤
የሱ መሆናችን ደስ ይለናል።
-
2. ዘላለም አምላካችንን ለማገልገል፣
በጸሎት ለሱ ቃል ገብተናል።
ወደር የለውም ደስታው፣
ውስጣዊ እርካታ ’ለው፣
ለቅኖች ቃሉን መስበክ፣
በአምላክ ስም መታወቅ።
(አዝማች)
ወደን ላምላክ ራሳችንን ወስነናል፤
የሱ መሆናችን ደስ ይለናል።
(በተጨማሪም መዝ. 43:3፤ 107:22ን እና ዮሐ. 6:44ን ተመልከት።)