መዝሙር 31
ከአምላክ ጋር ሂድ!
(ሚክያስ 6:8)
-
1. ካምላክ ጋር ሂድ ትሑት ሆነህ፤
ታማኝ ፍቅር ይኑርህ።
ካምላክ አትራቅ፤ ይሁን ወዳጅህ፤
እሱ ነው ኃይል ’ሚሰጥህ።
ያምላክን ቃል አጥብቀህ ያዘው፤
አትታለል በሰው።
ያምላክን እጅ አጥብቀህ ያዝ፤
በታማኝነት ታዘዝ።
-
2. ካምላክ ጋር ሂድ ንጹሕ ሆነህ፤
ከኃጢያት ድርጊት ርቀህ።
ፈታኝ ሁኔታ ቢያጋጥምህም
አምላክ አለ ከጎንህ።
ምስጋና ’ሚገባውን ነገር፣
እውነት የሆነውን፣
እነዚ’ን ሁሌ አውጠንጥን፤
አምላክ አብሮህ እንዲሆን።
-
3. ካምላክ ጋር ሂድ፤ ወዳጅህ ነው፤
በደስታ አገልግለው።
ስጦታው ብዙ፣ ወደር የሌለው፤
ምንጊዜም አመስግነው።
ይሖዋን ስታገለግለው
ልብህ ደስ ይበለው።
ደስታህን የሚያዩ ሁሉ
የሱ ’ንደሆንክ ያውቃሉ።
(በተጨማሪም ዘፍ. 5:24፤ 6:9ን፣ ፊልጵ. 4:8ን እና 1 ጢሞ. 6:6-8ን ተመልከት።)