በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 148

ይሖዋ ይታደጋል

ይሖዋ ይታደጋል

(2 ሳሙኤል 22:1-8)

  1. 1. ይሖዋ፣ ሕያው አምላክ መሆንህ ታይቷል፤

    ምድር፣ ሰማይ፣ ባሕር

    በሥራህ ተሞልቷል።

    እንዳንተ ያለ አምላክ

    ከቶ የለም።

    ጠላትም፣ ይጠፋል አይኖርም።

    (አዝማች)

    ይሖዋ ታማኞቹን ይታደጋል።

    ጠንካራ ዓለት እንደሆነ ያሳያል።

    ታምነን በሱ ክብሩን፣

    ዝናውን ’ናውጅ ላለም።

    ከፍ እናድርግ

    ያዳኛችንን ገናና ስም።

  2. 2. የሞት ገመድ ተብትቦኛል ስማኝ ’ባክህ፤

    “ድፍረት፣ ጥንካሬን ስጠኝ”

    ብዬ ስጮኽ፣

    “ከለላ ሁነኝ” ብዬ

    ስማጸንህ፣

    እባክህ ስማኝ ከመቅደስህ።

    (አዝማች)

    ይሖዋ ታማኞቹን ይታደጋል።

    ጠንካራ ዓለት እንደሆነ ያሳያል።

    ታምነን በሱ ክብሩን፣

    ዝናውን ’ናውጅ ላለም።

    ከፍ እናድርግ

    ያዳኛችንን ገናና ስም።

  3. 3. ነጎድጓድ ድምፅህ

    ሲሰማ ከማደሪያህ፣

    ጠላትህ ይርዳል፤

    ይደሰታል ሕዝብህ።

    የምትሻውን መሆን ትችላለህ፤

    መታደግህን

    ታሳያለህ።

    (አዝማች)

    ይሖዋ ታማኞቹን ይታደጋል።

    ጠንካራ ዓለት እንደሆነ ያሳያል።

    ታምነን በሱ ክብሩን፣

    ዝናውን ’ናውጅ ላለም።

    ከፍ እናድርግ

    ያዳኛችንን ገናና ስም።

(በተጨማሪም መዝ. 18:1, 2⁠ን እና 144:1, 2⁠ን ተመልከት።)