መዝሙር 145
አምላክ የሰጠው የገነት ተስፋ
-
1. በክርስቶስ ሺህ ዓመት ግዛት፣
ትሆናለች ምድር ገነት።
ኃጢያት፣ በደል ይደመሰሳል፤
ሥቃይ፣ ሞትም ይወገዳል።
(አዝማች)
ምድርን ገነት ያደርጋታል፤
በእምነት ዓይን ይታየናል።
ተስፋው በቅርብ ይፈጸማል፤
የገባው ቃል ይታመናል።
-
2. ሙታን በቅርብ ተስፋ አላቸው፤
ይነሳሉ፣ ዓላማው ነው።
‘በገነት ውስጥ ትኖራለህ’ ሲል
የአምላክ ልጅ ተስፋ ሰጥቷል።
(አዝማች)
ምድርን ገነት ያደርጋታል፤
በእምነት ዓይን ይታየናል።
ተስፋው በቅርብ ይፈጸማል፤
የገባው ቃል ይታመናል።
-
3. የአምላክ ልጅ ተስፋ ሰጥቶናል፤
የምድራችን ንጉሥ ሆኗል።
ምስጋናችን ላምላክ ይድረሰው፤
በየ’ለቱ ’ናወድሰው።
(አዝማች)
ምድርን ገነት ያደርጋታል፤
በእምነት ዓይን ይታየናል።
ተስፋው በቅርብ ይፈጸማል፤
የገባው ቃል ይታመናል።
(በተጨማሪም ማቴ. 5:5፤ 6:10ን እና ዮሐ. 5:28, 29ን ተመልከት።)