መዝሙር 140
መጨረሻ የሌለው ሕይወት
-
1. ይታይህ ባዲስ ዓለም፤
ሁሉም ሲኖር ዘላለም።
ሐዘን፣ ሥቃይ ተረስቶ፤
ሰላም፣ ደስታ ሰፍኖ።
(አዝማች)
ከልብ እንዘምር
ለዚህ ቀን ላበቃን።
መጨረሻ የሌለው፣
ሕይወት ልናገኝ ነው!
-
2. እርጅና ይወገዳል፤
ሰውም ፍጹም ይሆናል።
ነፃ ስንሆን ከችግር፣
አይኖር ለቅሶ፣ ሽብር።
(አዝማች)
ከልብ እንዘምር
ለዚህ ቀን ላበቃን።
መጨረሻ የሌለው፣
ሕይወት ልናገኝ ነው!
-
3. ሁላችን ገነት ገብተን፣
በደስታ እ’ኖራለን።
ለዘላለም ይሖዋን
’ናመሰግናለን።
(አዝማች)
ከልብ እንዘምር
ለዚህ ቀን ላበቃን።
መጨረሻ የሌለው፣
ሕይወት ልናገኝ ነው!