መዝሙር 101
በአንድነት አብሮ መሥራት
(ኤፌሶን 4:3)
-
1. አምላክ ወደ ቤቱ ጠራን፤
ከጨለማው ዓለም ወጣን።
ሰላም አንድነት አገኘን፤
በደስታም ተሞላን።
አንድነታችንን
እናደንቃለን።
ያምላክ ሥራ በዝቶልናል።
ልጁ ’ንዲመራን ተሹሟል።
በታዛዥነት አንድ ሆነን፣
’ናገልግል ይሖዋን።
-
2. ስንጸልይ ላንድነታችን፣
ስንጥር ደጎች ለመሆን፣
ያድጋል፣ ይበዛል ፍቅራችን፤
ደስታ፣ ሰላማችን።
ሰላም ያስደስታል፤
ልብ ያሳርፋል።
ወንድሞችን ከወደድን፣
እናገኛለን ሰላምን።
ባምላክ እርዳታ ተባብረን
’ናገለግላለን።
(በተጨማሪም ሚክ. 2:12ን፣ ሶፎ. 3:9ን እና 1 ቆሮ. 1:10ን ተመልከት።)